SAʴý

የእመቤታችን ኪዳነ ምሕረት መቅደስ በፔሌቮይሲን፣ ፈረንሳይ የእመቤታችን ኪዳነ ምሕረት መቅደስ በፔሌቮይሲን፣ ፈረንሳይ 

ቫቲካን በፈረንሳይ ፔሌቮይሲን ለእመቤታችን ኪዳነ-ምህረት ክብር የሚሰጥበት ቦታ እንዲሆን አጸደቀች።

እ.አ.አ በ1876 እስቴል ፌጌት የምትባል አንዲት ምስኪን ወጣት በአንዲት ትንሽዬ የፈረንሳይ ከተማ በሚገኘው የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ መቅደስ ውስጥ የእመቤታችን ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቅድስናን አስመልክቶ በቡርገስ ሊቀ ጳጳስ የቀረበውን በላቲን ቋንቋ “ኒሂል ኦብስታት” (ምንም የምያደናቅፍ ነገር የለውም) በማለት የእምነት አስተምህሮ የሚከታተለው የቅድስት መንበር ጽሕፈት ቤት ፈቃዱን መስጠቱን የገለጸ ሲሆን ይህች ወጣት ፌጌት የምትባል ልጅ የድንግል ማርያምን በርካታ መገለጦች አይታ እንደ መሰከረችም ተዘግቧል።

የዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ-ቫቲካን

"ምንም እንኳን አሁን ያለው ተግባር ባይሆንም" የእምነት አስተምህሮን የሚመለከተው የቅድስት መንበር ጽሕፈት ቤት "ከተፈጥሮ በላይ በሆነው ባህሪ ወይም መለኮታዊ አመጣጥ ላይ ያለውን አስተያየት ለመግለጽ ከተፈጥሮ በላይ የሆኑ ክስተቶች እና መልእክቶች፣ በኤስቴል ከድንግል ማርያም እንደመጡ ያቀረቧቸው መግለጫዎች አሉ፣ በዚህ መንፈሳዊ ልምምድ መካከል የመንፈስ ቅዱስን ተግባር እንድንመለከት የሚያስችለን ልዩ እሴት አለው" ሲል ይህንን በተመለከተ ባወጣው መግለጫ ገልጿል።

ብፁዕ ካርዲናል ቪክቶር ማኑኤል ፈርናንዴዝ በመካከለኛው ፈረንሳይ በምትገኝ በፔሌቮይሲን መቅደስ በምትገኝ ትንሽ ከተማ እ.አ.አ በ1876 ዓ.ም አንዲት ምስኪን ወጣት ሴት ኢስቴል ፌጌት ስለተከበረችው "የምሕረት እመቤታችን" በላቲን ቋንቋ "ኒሂል ኦብስታት" (ምንም የምያደናቅፍ ነገር የለውም) የተሰኘውን ፈቃድ በላኩት  ደብዳቤ ላይ ይህን ጽፈዋል። "የድንግል ማርያምን ብዙ መገለጦች አጋጥሟታል" ሲሉ መግለጫው አክሎ ገልጸዋል።

ደብዳቤው ለፈረንሳዩ የቡርጅ ሊቀ ጳጳስ ጄሮም ዳንኤል ቢው የተላከ ሲሆን ይህም ሐሙስ ነሐሴ 23/2024 ዓ.ም በርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ ተቀባይነት አግኝቷል።

የሚመከር አምልኮ

በደብዳቤው ላይ የእምነትን አስተምህሮን የሚመለከተው የቅድስት መንበር ጽሕፈት ቤት ዋና ጸኃፊ "በዚህ መንፈሳዊ ክስተት ላይ ምንም አይነት አስተምህሮ፣ ሞራላዊ ወይም ሌሎች ተቃውሞዎች የሉም" ብቻ ሳይሆን ምእመናን "በዚህም ላይ ጠበቃ ሆነው እንዲገኙ ስልጣን እንደተሰጣቸው አረጋግጠዋል። ጥንቃቄ በተሞላበት መንገድ እንዲጓዙም ይመከራሉ” ሲሉ አክሎ ገልጿል። “ነገር ግን፣ በዚህ ጉዳይ ላይ፣ ቀድሞውንም እየበለጸገ ያለው እመነት—በተለይ በነፃነት እሱን ለመከተል ለሚፈልጉ ሁሉ ይመከራል" ሲል ጽሕፈት ቤቱ አክሎ ገልጿል።

ለእመቤታችን ኪዳነ ምህረት ያለንን አክብሮ ማስቀጠል የሚመከር ጉዳይ ነው ብለዋል ካርዲናል ፈርናንዴዝ “መንፈሳዊ የዋሕነት የመተማመን እና የፍቅር መንገድ” ስለሚሰጥ ብዙ የሚጠቅም እና “ለቤተክርስቲያኗ ሁሉ የሚጠቅም ነው ብለዋል።

የኤስቴል መልእክት ለቅድስት ድንግል

ኤስቴል እ.አ.አ በመስከረም 12/1843 ዓ.ም በጣም ድሃ ከሆነ ቤተሰብ ተወለደች። እራሷን እና ወላጆቿን ለመርዳት በመጀመሪያ የልብስ ማጠብ አገልግሎት ትሰጥ ነበር፣ ከዚያም አገልጋይ ሆና ሠርታለች።

በጠና ታማ በሞት አደጋ ላይ ወድቃ ድሆች ወላጆቿን መደገፏን እንድትቀጥል ድንግል ማርያም ስለ ፈውሷ ልባዊ ደብዳቤ ለመጻፍ ወሰነች።

ቃላቶቿ፣ ካርዲናል እንዲህ ሲሉ ጽፈዋል፣ “በቀላልነታቸው፣ ግልጽነታቸው እና ትህትናቸው አስደናቂ ናቸው።

በመቀጠልም “ኤስቴል ህመምዋ ያስከተለውን ስቃይ ትናገራለች። በስቃዩዋ የተነሳ ክርስቲያናዊ ሕይወቷን እተዋለሁኝ ብላ አልተመጻደቀችም።  በተቃራኒው የህይወት እቅዷ ለሚያስተጓጉል በሽታ በውስጧ መቋቋሟን ትገልጻለች ሲሉ ተናግረዋል።

በመጨረሻ የእምነት አስተምህሮን የሚከታተለው የቅድስት መንበር ጽሕፈት ቤት እንዳመላከተው ከሆነ  ሁልጊዜም ለእግዚአብሔር ፈቃድ ትገዛለች እና አባቷን እና እናቷን  በጥንካሬ ብቻ መርዳት ትፈልጋለች" ሲል ጽሕፈት ቤቱ የገለጸ ሲሆን “ለሌሎች መስጠት ለጋስ መሰጠት ነው፣ ሌሎችን ለመንከባከብ የሚያገለግለው ይህ ሕይወት የእናትን ልብ በጣም የነካው ነው:- 'እናት ከንግግራችን በስተጀርባ የተደበቁትን መልካም ነገሮች እንዴት ማወቅ እንደምትችል ታውቃለች" ሲል ገልጿል።

ተአምራዊ ፈውስ

ወጣቷ ሴት በየካቲት ወር 1876 በ 32 ዓመቷ የመጀመሪያዎቹ የማርያም መገለጾችን ማየት መጀመሯን  ገልጻለች። በአምስተኛው መገለጥ፣ ቅድስት እናት ቃል እንደገባችው፣ ሙሉ በሙሉ ተፈወሰች።

በነዚህ መልእክቶች፣ ካርዲናል እንደተመለከቱት፣ “ሁሉም ነገር የክርስቶስ ነው። የኤስቴል ፈውስ እንኳን በቀጥታ የማርያም ሳይሆን የእናቱን አማላጅነት የሰማው ክርስቶስ ነው” በማለት ተናግሯል።

 

30 August 2024, 16:07