SAʴý

ር.ሊ.ጳ ፍራንችስኮስ ጌታ በውስጣችን የዘራው ዘር እስኪበቅል በትዕግስት ይጠብቃል ማለታቸው ተገለጸ!

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ ዘወትር እሁድ እለት በቫቲካን በሚገኘው በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ለሚሰበሰቡ ምዕመናን በእለቱ ቅዱስ ወንጌል ላይ ተንተርሰው የቅዱስ ወንጌል አስተንትኖ እንደሚያደርጉ ይታወቃል። በዚህ መሰረት ቅዱስነታቸው በሰኔ 09/2016 ዓ.ም ባደረጉት የቅዱስ ወንጌል አስተንትኖ ጌታ በውስጣችን የዘራው ዘር እስኪበቅል ድረስ በትዕግስት ይጠብቃል ማለታቸው ተገልጿል።

የእዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ-ቫቲካን

ክቡራን እና ክቡራት የዝግጅቶቻችን ተከታታዮች ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ በወቅቱ ያደረጉትን የቅዱስ ወንጌል አስተንትኖ ሙሉ ይዘቱን እንድሚከተለው አሰናድተነዋል፣ ተከታተሉን።

የተወደዳችሁ ወንድሞቼ እና እህቶቼ እንደምን አረፈዳችሁ!

በዛሬው እለት የስርዓተ አምልኮ ላይ የተነበበው ቅዱስ ወንጌል ስለ እግዚአብሔር መንግሥት በዘር አምሳል ይነግረናል (ማር. 4፡26-34)። ኢየሱስ ይህንን ምሳሌ ደጋግሞ ተጠቅሞበታል (ማቴ 13፡1-23፤ ማር 4፡1-20፤ ሉቃ. 8፡4-15) እናም ዛሬ ይህን የሚያደርገው ከክርስቶስ ጋር በተገናኘ አንድ አስፈላጊ አመለካከት ላይ እንድናሰላስል በመጋበዝ ነው። የዘሩ ምስል፡ በራስ የመተማመን መንፈስ ነው።

በእርግጥም በሚዘራበት ወቅት ገበሬው የቱንም ያህል ጥሩ ወይም የበዛ ዘር ቢበተን ወይም መሬቱን የቱንም ያህል ቢያዘጋጅ እፅዋቱ ወዲያው አይበቅልም፥ ጊዜ ይወስዳል እና ትዕግስት ይጠይቃል! ስለዚህ ከተዘራ በኋላ ፣ ዘሮቹ በትክክለኛው ጊዜ እንዲከፈቱ እና ቡቃያው ከዘሩ ውስጥ ወጥቶ እንዲበቅል እና እንድያብብ፣ በመጨረሻ ፣ የተትረፈረፈ መኸር (ሉቃስ 8፡ 28-29) እስኪያገኝ ድረስ ዋስትና ለመስጠት በጥንካሬ እና በድፍረት እንዴት መጠበቅ እንዳለበት ያውቃል ። ከመሬት በታች ያለው ተአምር በሂደት ላይ ነው (ሉቃስ 8፡ 27)፣ ትልቅ እድገት አለ፣ ነገር ግን የማይታይ ነው፣ ትዕግስት ይጠይቃል፣ እና እስከዚያው ድረስ መሬቱን መንከባከብ፣ ውሃ ማጠጣት እና መሬቱን ከአረም መጠበቅ ያስፈልጋል። ምንም እንኳን በገጹ ላይ ምንም እየተከሰተ ያለ ባይመስልም ።

የእግዚአብሔር መንግሥትም እንዲሁ ነው። ጌታ በውስጣችን የቃሉን እና የጸጋውን ዘር፣ መልካም ዘሮችን፣ የተትረፈረፈ ዘርን ያስቀምጣል፣ እናም ከዛም ከእኛ ጋር መሄዱን ሳያቋርጥ በትዕግስት ይጠብቃል። ጌታ እኛን መንከባከብ ይቀጥላል፣ በአባትነት እምነት፣ ነገር ግን ጊዜን ይሰጠናል - ጌታ ታጋሽ ነው - ዘሩ እንዲከፈት፣ እንዲያድግ እና እንዲያብብ የመልካም ስራ ፍሬዎችን እስክያፈራ ድረስ ይታገሳል። ይህ ደግሞ በመሬቱ ውስጥ ምንም ነገር እንዲጠፋ ስለማይፈልግ፣ ሁሉም ነገር ወደ ሙሉ ብስለት እንዲደርስ፣ ሁላችንም እንደ ዘሩ እንድናብብ እና እንድናድግ ይፈልጋል።

ይህ ብቻ አይደለም። ይህንን በማድረጋችን ጌታ ምሳሌ ይሰጠናል፡- እኛም ባለንበት ቦታ ሁሉ ወንጌልን እንድንዘራ፣ ከዚያም የተዘራው ዘር እንዲያድግና በእኛም ሆነ በሌሎች ውስጥ እንዲያፈራ እንድንጠብቅ ያስተምረናል እናም ተስፋ ሳንቆርጥ እና መደጋገፍና መረዳዳትን ሳናቋርጥ ምንም እንኳን ጥረታችን ብያስፈልግም ፈጣን ውጤት የምናገኝ አይመስልም። እንድያውም ብዙ ጊዜ በመካከላችን እንኳን ከመታየት ባለፈ ተአምር እየተሠራ ነው በጊዜውም ብዙ ፍሬ ያፈራል!

ስለዚህም ራሳችንን ልንጠይቅ እንችላለን፡- ቃሉ በእኔ ውስጥ ይዘራልን? እኔስ የእግዚአብሔርን ቃል በምኖርባቸው ቦታዎች በመተማመን እዘራለሁን? በትዕግስት እጠብቃለሁ ወይንስ ውጤቱን ወዲያውኑ ስላላየሁ ተስፋ ቆርጫለሁ? ወንጌልን ለመስበክ የተቻለኝን እያደረግሁ ሁሉንም ነገር በጸጥታ ለጌታ እንዴት እንደምሰጥ አውቃለሁን?

የቃሉን ዘር በውስጧ ተቀብላ ያሳደገች ድንግል ማርያም ለጋስና ታማኝ የወንጌል ዘሪዎች እንድንሆን በአማላጅነቷ እርሷ ትርዳን።

16 June 2024, 16:00

የገብርኤል ብሥራት ጥንታዊ መሠርት የያዘና የጌታችን እየሱስ ክርስቶስን ሰው መሆን በማስታወስ በቀን ሦስት ጊዜ ማለትም በንጋት (በአስራሁለት ሰዓት) በቀትር (በስድስት ሰዓት) እንዲሁም በማታ (በአስራሁለት ሰዓት) የሚደገም የጸሎት ዓይነት ሲሆን ጸሎቱ በሚደገምበት ሰዓት ቤተ ክርስቲያንም የመልኣከ እግዚኣብሔርን ደወል በዚሁ ሰዓት ትደውላለች። ይህ ጸሎት መልኣከ እግዚኣብሔር የሚለውን ስያሜ ያገኝው ከጸሎቱ ከመጀመሪያ ስንኝ የእግዚኣብሔር መልኣከ ማርያምን አበሠራት ከሚለው የተወሰደ ሲሆን ጸሎቱ ስለ ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ ሰው መሆን ይናገራል። ጸሎቱ በሦስት የተከፈሉ አጫጭር ስንኞች ሲኖሩት በእነኚህ በሦስት አጫጭር ስንኞች መሓል ጸጋን የተሞላሽ የሚለው የማርያም ጸሎት ይደገማል። ይህ ጸሎት በሰንበትና በበዓላት ዕለት ልክ በእኩለ ቀን ላይ በዕለቱ ወንጌል ላይ ትንሽ አስተምሮና ገለፃ ከሰጡ በኋላ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት በቅዱስ ጴጥሮስ ኣደባባይ ላይ ይህንን ጸሎት ይመራሉ። በመቀጠልም በአደባባዩ ላይ የተገኝው ከተለያየ ቦታ ለንግደት የመጣውን ሕዝብ ሰላምታ ይሰጣሉ።በየትኛውም ጊዜ ከበዓለ ፋሲካ እስከ በዓለ ጰራቅሊጦስ በመልኣከ እግዚኣብሔር ጸሎት ፈንታ የጌታችን እየሱስ ክርስቶስን ትንሣኤ የሚዘክረውን “የሰማይ ንግሥት ሆይ ደስ ይበልሽ” የሚለው ጸሎት የሚደገም ሲሆን በመሓል በመሓሉ ጸጋን የተሞላሽ ማርያም ሆይ የሚለው ጸሎት ይታከልበታል።

መልኣኩ ገብርኤል ማሪያምን አበሰራት የሚለው የቀርብ ጊዜ ጸሎት

ሁሉንም ያንብቡ >